FREE TENDER | ነፃ ጨረታ
ቀጥሎ የቀረበው ጨረታ ክፍያ የማይጠይቅና አባል መሆን ሳይጠበቅብዎት የሚመለከቱት ነፃ ጨረታ ነው ሌሎች ሁሉንም ጨረታዎች ለማግኘት በዋልያ ቴንደር ደንበኛ አካውንትዎ እዚህ ይግቡ አባል ካልሆኑ እዚህ ይመዝገቡ
These tenders are free to view. You don't need to be a walia tender member to view them.
ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
የግዥው መለያ ቁጥር -LS/C F/E/D 02/2015
በልደታ ክፍለ ከተማ ወ/6/ፋ/ጽ/ቤት- አስተዳደር ጽህፈት ቤት ስር ላሉት ጽህፈት ቤቶች በ2015 ዓ.ም. በጀት አመት የሚያስፈልጋቸውን
- ሎት1. የትራንስፖርት አገልግሎት የጨረታ ማስከበሪያ ብር 2,000
- ሎት2. የጽህፈት መሳሪያ የጨረታ ማስከበሪያ ብር 7,000
- ሎት3. የደንብ ልብስ እና የደንብ ልብስ ስፌት የጨረታ ማስከበሪያ ብር 7,000
- ሎት4. የጽዳት እቃዎች የጨረታ ማስከበሪያ ብር 7,000
- ሎት5. ኤሌክትሮኒክስ ጥገና የጨረታ ማሰከበሪያ ብር 3,000
- ሎት6. ህትመት የጨረታ ማሰከበሪያ ብር 3,000
- ሎት7. ቋሚ እቃ የጨረታ ማሰከበሪያ ብር 10,000
- ሎት8. ምርጥ ዘሮች የጨረታ ማሰከበሪያ ብር 1,000
ብቃት ያላቸውንና በመስኩ የተሰማሩ ተጫራቾችን አወዳድሮ ግዥ መፈጸም ይፈልጋል።
በዚህም መሰረት፡
- በጨረታው ለመወዳደር ፍላጎት ያላቸው ተጫራቾች የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያላቸው ፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉ ፣ በመንግስት ግ/ን/አስ/ኤጀንሲ ድረ ገጽ ላይ በአቅራቢዎች ምዝገባ ዝርዝር የተመዘገቡ ፣ የቲን እና የቫት ተመዘጋቢ የሆኑና የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ
- ተጫራቾች የጨረታው ማስከበሪያ በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ከጨረታው ሰነዳቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቾች ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት እለት አንስቶ በተከታታይ 10 የስራ ቀናት የማይመለስ ብር 200 በመክፈል በልደታ ክፍለ ከተማ/ወ/6/ፋ/ጽ/ቤት ቢሮ 3ኛ ፎቅ በመምጣት የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ።
- ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዳቸውን በታሸገ ኤንቨሎፕ ማስታወቂያው ከወጣበት እለት ጀምሮ ለተከታታይ 10 የስራ ቀናት በወረዳው ቢሮ 3ኛ ፎቅ ለጨረታ በተዘጋጀ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በአስራ አንደኛው ቀን በ4፡00 ሰአት ታሽጎ በእለቱ ከጠዋቱ 4፡30 ሰዓት ይከፈታል። የመክፈቻ ቀኑ ቅዳሜና እሁድ ወይም የበአል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰአት ታሽጎ ይከፈታል።
- ተጫራቾች የጨረታ ሳጥን ከመከፈቱ በፊት ለተወዳደሩባቸው ሎት-2- ሎት-3- ሎት-4 - ሎት-6 ናሙና ማቅረብ የሚኖርባቸው ሲሆን- በቀረበው የፍላጎት መግለጫ መሰረት የተሟላ የፍላጎት መግለጫ ማዘጋጀትና ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የሚወዳደሩባቸውን እቃዎች ለእያንዳንዱ ከቫት ጋር ያለውን ዋጋ ማስቀመጥ ይጠበቅባቸዋል።
- የዘገየ ጨረታና በጨረታ መክፈቻ ላይ ያልተነበበ ጨረታ ተቀባይነት የለውም።
- አሸናፊ ተጫራቾች ያሸነፉባቸውን እቃዎች በራሳቸው ትራንስፖርት ግዥ ፈጻሚው መስሪያ ቤት ድረስ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።
- መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
በተጨማሪ ለማብራሪያ ጥያቄ ለጨረታው ከቀረቡ የእቃዎች ዝርዝር ውስጥ መ/ቤቱ እስከ 20 በመቶ ለመጨመር ወይም ለመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው::
የመ/ቤቱ ስልክ ቁጥር-011 385 17 98
አድራሻ - ልደታ ክ/ከተማ ወረዳ 6 አስተዳደር ብስራተ ገብርኤል ገባ ብሎ ሽመክት የገበያ ማዕከል ህንጻ 3ኛ ፎቅ
በልደታ ክፍለ ከተማ የወ6 ፋይናንስ ጽ/ቤት
በኢትዮጵያ ውስጥ በየእለቱ የሚወጡ ጨረታዎች እንዲደርስዎት የዋልያ ቴንደር አካውንት ይክፈቱ ወይም በ 0942125616 ይደውሉልን በቀላሉ እኛ አካውንት እንሰጥዎታለን
ምንም አይነት ጨረታ ማስታወቂያ አያመልጥዎትም!!
የሚከፈለውም በባንክ (ሞባይል ባንኪንግ፣ቀጥታ በባንክ ትራንስፈር፣ቴሌብር፣ሲቢኢ ብር ...የመሳሰሉት ፣ አሊያም በአካል
ቃሊቲ ቶታል ካፍደም ፕላዛ 4ኛ ፎቅ f425 )