FREE TENDER | ነፃ ጨረታ
ቀጥሎ የቀረበው ጨረታ ክፍያ የማይጠይቅና አባል መሆን ሳይጠበቅብዎት የሚመለከቱት ነፃ ጨረታ ነው ሌሎች ሁሉንም ጨረታዎች ለማግኘት በዋልያ ቴንደር ደንበኛ አካውንትዎ እዚህ ይግቡ አባል ካልሆኑ እዚህ ይመዝገቡ
These tenders are free to view. You don't need to be a walia tender member to view them.
ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ በመከላከያ ዋር ኮሌጅ ግቢ ለሚያስገነባው ግንባታ የሴራሚክ እና የግራናይት ማንጠፍ ስራ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል። ስለዚህ በዘርፉ የተሰማራችሁ ደረጃ 6 እና ከዚያ በላይ የሆናችሁ ተጫራቾች በጨረታው መሳተፍ የምትችሉ ሲሆን ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ቅዳሜን ጨምሮ ባሉት ተከታታይ 10 የሥራ ቀናት ውስጥ የጨረታውን ሰነድ በመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ መከላከያ ዋር ኮሌጅ ፕሮጀክት አቅርቦት እና ግዥ ቢሮ በአካል በመቅረብ ሰነዱን በግዛት መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እያሳወቅን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ጨረታው በ10ኛው ቀን በ8፡00 ሰዓት ላይ ተዘግቶ በ8፡15 የሚከፈት ሲሆን 10ኛው ቀን በዓል ወይም እሁድ ቀን ከዋለ በማግስቱ በ8፡00 ሰዓት ላይ ተዘግቶ በ8፡15 የሚከፈት ይሆናል።
ተጫራቾች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች ማሟላት ይጠበቅባቸዋል።
ማሳሰቢያ፡_
- የታደሰ የንግድ ፍቃድ
- የግብር ከፋይ (Tin No.) ኮፒ ይያያዝ፤
- ቫት ተመዝጋቢ የምስhር ወረቀት ያለው፤
- የምዝገባ ሰርተፊኬት መቅረብ አለበት፤
- ፕሮጀክቱ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ብር 100 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል መውሰድ የምትችሉ መሆኑን እናሳውቃለን።
አድራሻ፡- ቆሪ አደባባይ
ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር፡_ 011 872 8303/011 872 1174
የመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ
በኢትዮጵያ ውስጥ በየእለቱ የሚወጡ ጨረታዎች እንዲደርስዎት የዋልያ ቴንደር አካውንት ይክፈቱ ወይም በ 0942125616 ይደውሉልን በቀላሉ እኛ አካውንት እንሰጥዎታለን
ምንም አይነት ጨረታ ማስታወቂያ አያመልጥዎትም!!
የሚከፈለውም በባንክ (ሞባይል ባንኪንግ፣ቀጥታ በባንክ ትራንስፈር፣ቴሌብር፣ሲቢኢ ብር ...የመሳሰሉት ፣ አሊያም በአካል
ቃሊቲ ቶታል ካፍደም ፕላዛ 4ኛ ፎቅ f425 )