ኢትዮ ቴሌኮም ደቡብ ምስራቅ ሪጅን ለተለያዩ የመ/ቤቱ ስራ የሚውሉ መኪኖችን በጨረታ አወዳድሮ ለመከራየት ይፈልጋል፡፡ RFQ 4248975 በዚሁ መሰረት በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልግ ድርጅት ከታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟላ ሰነዱን በመግዛት መወዳደር ይችላል፡፡
1. ተጫራቾች ዝርዝር መግለጫ የያዘውን የጨረታ ሰነድ መግዛት የሚችሉት ከህዳር 03 ቀን 2016 ዓ.ም እስከ ህዳር 20 ቀን 2016 ዓ.ም ከሰኞ እስከ ዓርብ በስራ ሰዓት አዳማ ከተማ ኦሮሚያ ልማት ማህበር ህንጻ 5ኛ ፎቅ ላይ በሚገኘው የመስሪያ ቤቱ ሶርሲንግ ክፍል በመቅረብ ስለጨረታው መረጃ ማግኘትና የማይመለስ ብር 300.00 (ሶስት መቶ) ብር በመክፈል የጨረታውን ሠነድ በመግዛት መወዳደር ይችላሉ፡፡
2. ማንኛውም ተጫራቾች የጨረታ ሰነድ ለመግዛት በሚመጡበት ወቅት የዘመኑን ግብር የከፈሉና የታደሰ የንግድ ፈቃድ ማስረጃ ዋናውን እና ኮፒ ይዘው መቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
3. ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ ውጤቱ እንደታወቀ የሚመለስ የጨረታ ማስከበሪያ ከታወቀ ባንክ ተረጋግጦ በሚቀርብ ዋስትና (CPO) 50,000 (ሀምሳ ሺህ ብር) ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
4. ተጫራቾች በጨረታ ሰነዶቻቸው ላይ የጨረታውን ስም፤ የተጫራቹን ሙሉ ስም እና አድራሻ በትክክል መጻፍ አለባቸው፡፡
5. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ህዳር 20 ቀን 2016 ዓ.ም ከረፋዱ 5፡oo ሰዓት ተዘግቶ በዕለቱ ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ይከፈታል፡፡
6. ተጫራቾች የወሰዱትን የጨረታ ሰነድ ሲሞሉ ስርዝ ድልዝ ያለው ሰነድ ተቀባይነት የለውም፡፡
7. መስሪያ ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱንና ሲፒኦ በታሸገ ኤንቨሎፕ አድርገው ለዚሁ በተዘጋጀ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
ስተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 022-111-09-94/ 022-112-35-50 ደውሎ መጠየቅ
ደቻሳስ፡፡